ስለ እኛ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን እንደገና ለማዋቀር ባወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016 ከተዋቀሩ አስፈፃሚ አካላት አንዱ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ነው፡፡
መስሪያ ቤቱ በሁለት ዘርፍ ተዋቅሮ በአራት ዳይሬክቶሬቶች እና በአስር ቡድኖች በማዕከል ደረጃ የሚመራ ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ ዘመናዊ የመንግስት ህንጻና ንብረት አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋት ወጥና ስታንዳርዱን የጠበቀ፣ ደህንነታቸው የጠበቀ ፣ፅዱና ምቹ የሆነ ምድረ ግቢ ያላቸው ህንፃዎችን በማልማት ቀልጣፋና ውጤታማ የአሰራር ስርዓት እንዲኖር የቁጥጥር ስርዓት በመዘርጋት ከብክነት የፀዳ የንብረት አስተዳደር ስርዓት ማስፈን ነው፡፡ በተጨማሪም የህንፃና የንብረት አስተዳደር ስርዓቱን ለማዘመን፣የተደራጀ ተዓማኝነት ያለው የመረጃ አያያዝ ስርዓት ስራ ላይ ለማዋል፣ ንብረቶችን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በማድረግ የሀብት ብክነትን በመከላከል ፍትሃዊ የሆነ የሀብት አጠቃቀም የከተማ አስተዳደሩን ህንፃዎችና ንብረቶች የማስተዳደር፣ የመቆጣጠር፣ የመከታተል፣ የቢሮ መገልገያ እቃዎች ስታንዳርዶችን የማዘጋጀትና የማስተግብር፣ዘመናዊ የንብረት አስተዳደር አሰራሮች የማስተግበር ፣የአቅም ግንባታ ስራዎች በማከናወን ለከተማ አስተዳደሩ የቴክኒክና ሙያዊ ድጋፍ የመስጠት ስራዎችን የሚያከናውን ተቋም ነው፡፡